በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው ቱም አውሮፕላን ማረፊያ በማጂ ቱም ከተማ የአስተዳደር ማዕከል ለሆነው ቱም እና ማጂ ከተሞች እንደ ወሳኝ አገናኝ ሆኖ ሲገለግላል ነበር ፤ ከባህር ጠለል በላይ በ4,650 ጫማ (1,417 ሜትር) ከፍታ ያለው ይህ የህዝብ አውሮፕላን ማረፊያ እንደ ማጂ ላሉ ራቅ ላሉ የሀገራችን ክፍሎች ከትላልቅ የከተማ አካባቢዎች ጋር በማገናኘት ረገድ ወሳኝ ሚና ሲጫወት ቆይቷል።.
አውሮፕላን ማረፊያው 3,051 ጫማ (930 ሜትር) ርዝመት ያለው የሳር ወለል ማኮብኮቢያ አለው። በታሪክ ቱም አውሮፕላን ማረፊያ በኢትዮጵያ አየር መንገድ አገልግሎት ይሰጥ ስለነበር በ1980ዎቹ እና 1990ዎቹ ለነዋሪዎች አስፈላጊ የመጓጓዣ ዘዴ እንዲሆን አድርጎታል። ይሁን እንጂ ለዓመታት ኤርፖርቱ አገልግሎት ውጭ በመሆን ላይ ይገኛል ።.
በአሁኑ ወቅት ቱም ኤርፖርትን ለመክፈት በመንግስት እቅድ እንዳለ ሆኖ ፣ ይህ ተነሳሽነት ሀገራዊ ትስስርን ለማጎልበት እና በአካባቢው ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማነቃቃት ሰፊ እድል እንዳለ ያሳያል። ብዙ ነዋሪዎች የኤርፖርቱ መከፈት የአየር ትራንስፖርት ተደራሽነትን ከማደስ ባለፈ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም እና ንግድን እንደሚያሳድግ ተስፋ ሰጪ ነው።.
የአውሮፕላን ማረፊያው ስትራቴጅካዊ አቀማመጥ ምቹ እና የአከባቢውን የተፈጥሮ ውበት ፣ የባህል እና ብሄራዊ ፓርክ እምቅ ሀብት ለመቃኘት ለሚፈልጉ መንገደኞች መግቢያ በር በመሆን አቅም ይጨምራል። በአካባቢው ማህበረሰብ በአንድ ወቅት መደበኛ መጓጓዣ አማራጭ ሆኖ ያገለገለው የትራንስፖርት መስመር ዳግም ተጠቃሚ ለመሆን በጉጉት በመጠባበቅ ላይ ያለ እና እንደ ብሩህ ተስፋ የሚታይ ነው።